የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች 6ኛው ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 6ኛው ልዩ ስብሰባ፤ በወቅታዊ የፀጥታ እና በንጹሐን ዜጎች ጉዳይ ላይ ተወያይቶ በምክር ቤቱ የበላይ አመራር የሚሰየሙ እና ብዝኀነትን ታሳቢ ያደረገ ልዩ ኮሚቴ የዜጎችን ጭፍጨፋ እንዲመረምር ውሳኔ አስተላልፏል።
የዕለቱን መርኃ-ግብር በግፍ ለተጨፈጨፉት ዜጎች የአንድ ደቂቃ የኅሊና ጸሎት በማድረግ የጀመረው ምክር ቤቱ፤ የሚከተሉትን የውሳኔ ሐሳቦች አስተላልፏል፡፡
በዜጎች ላይ የተፈጸመውን ጭፍጨፋ እጅግ የኮነነው ምክር ቤቱ፤ በአገራችን በየትኛውም ክልልና አካባቢ በሲቪል ዜጎች ላይ የሞትና የአካል ጉዳት ያስከተሉ እና ንብረት ያወደሙ ግለሰቦች በሕግ እንዲጠየቁ እንዲደረግ ሲል ውሳኔ አሳልፏል።
በየደረጃው ያለው አመራር አካል፣ የጸጥታ አካል እና የፍትሕ ተቋም የህዝቡን ደህንነትና ሠላም በጥብቅ እንዲያስከብር፣ አጥፊዎች ለሕግ ተጠያቂነት እንዲቀርቡ እንዲደረግ ወስኗል።
ከመንደራቸውና ከቀያቸው የተፈናቀሉ ዜጎችን መልሶ የማቋቋም ሥራ በአስቸኳይ እንዲሰራ የወሰነው ምክር ቤቱ፤ የኢትዮጵያ ህዝቦች በዚህ በአስቸጋሪ ወቅት ከየትኛውም ጊዜ በላይ በወንድማማችነት፣ በአብሮነት እና በአንድነት እንዲቆሙ መልዕክቱን አስተላልፏል።
መለያና ስያሜ
በግብርና ምርቶቹ ብራንድ ይፋ ማድረጊያ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት በግብርና ሚኒስቴር የኢንቨስትመንትና ግብዓት ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ ሶፍያ ካሳ (ዶ/ር) "ዛሬ ብራንድ የተደረጉ ምርቶች በግብርና ሚኒስቴር በአስር ዓመታት ውስጥ ትኩረት ተሰጥቷባቸው በትኩረት እየሰራባቸው ያሉ ስትራቴጂክ ምርቶች ናቸው" ብለዋል።
ምርቶቹ ብራንድ እንዲደረጉ ሃሳቡን ላመነጩት እና እንዲተገበር ላደረጉት የኢትዮጵያ ኅብረት ስራ ኮሚሽን ኮሚሽነር ወ/ሮ ፍሬዓለም ሺባባዉም ምስጋና አቅርበዋል።
የግብርና ምርቶቹ ብራንዶች ይፋ በሆኑበት መርሃ ግብር በምርቶቹ እሴት ሠንሠለቶች ደካማ የግብይት ትስስር፣ የገበያ መሰረተ ልማት እጦት እና በእሴት ሰንሰለት ውስጥ ገበያውን የሚያዛቡ ግለሰቦችና ቡድኖች እንዳሻቸው ዋጋ መተመናቸውን እንዲያቆሙ በኅብረት ስራ ፣ በንግዱ ዘርፎች ያሉ እና ሌሎች ባለድርሻ አካለት ርብርብ እና ቅንጅት ችግሮች መፈታት እንዳለባቸው ተገልጧል፡፡

Source: P.Record
በብራንድ ይፋ ማድረጊያ ስነ ስርዓቱ ላይ የደቡብ ክልል እና የአማራ ክልል የኅብረት ስራ ኤጀንሲ ሃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
በቀጣይም በሶማሌ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና ኦሮሚያ ክልሎች በቅደም ተከተል የሚገኙት የፍየል፣ ማንጎና ቀይ ሽንኩርት ምርቶች ብራንድ ለማድረግ የኢትዮጵያ ኅብረት ስራ ኮሚሽን እንቅስቃሴ መጀመሩ አስታውቋል።

Officials. Source: P.Record
ብራንድ የተደረጉት ምርቶች በኢትዮጵያ ኀብረት ሥራ ኮሚሽን አነሳሽነት በአይነታቸው የተለዩ በኀብረት ሥራ ማኅበራት አባላት የሚመረቱ መሆኑን ኤጀንሲው አስታውቋል፡፡