የአዲሱ የኢትዮጵያ መንግሥት ካቢኔ አባላት ሹመቶች በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፅድቅ ተቸራቸው

*** የካቢኔ አባላት ሹመቱቶቹ በአብላጫ ድምፅ የፀደቁት 2 ተቃውሞና 12 ድምፀ ተአቅቦ ገጥሟቸው ነው

Homeland Report

Newly elected parliament members of Ethiopia participate during the swearing-in ceremony, in the city of Addis Ababa, Ethiopia, on October 04, 2021. Source: Getty

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ኦክቶበር 06 ያቀረቡት የካቢኔ አባላት ሹመቶች በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይሁንታን አግኝቷል።

በአብላጫ ድምፅ ይሁንታ የተቸራቸው ሾመቶች በድምፅ አሰጥታ ወቅት 2 ተቃውሞና 12 ድምፀ ተአቅቦ አግኝቷቸዋል።

በዚህም መሠረት፦

  •  ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር - ደመቀ መኮንን
  • መከላከያ ሚኒስትር - ዶ/ር አብረሃም በላይ
  • የገንዘብ ሚኒስትር - አህመድ ሽዴ
  • የሥራና ክህሎት ሚኒስትር - ሙፈሪሃት ካሚል
  • ግብርና ሚኒስትር - ኡመር ሁሴን
  • የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር - ኢ/ር አይሻ መሃመድ
  • የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር - ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ
  • የትምህርት ሚኒስትር - ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ
  • የትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ሚኒስትር - ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ
  • የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር- አቶ ገብረመስቀል ጫላ
  • የኢንዱስትሪ ሚኒስትር- አቶ መላኩ አለበል
  • የሰላም ሚኒስትር- አቶ ብናልፍ አንዷለም
  • የፍትህ ሚኒስትር- ዶ/ር ጌዴዎን ጤሞጢዎስ
  • የጤና ሚኒስትር- ዶ/ር ሊያ ታደሰ
  • የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር- አቶ በለጠ ሞላ
  • የቱሪዝም ሚኒስትር- አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ
  • የገቢዎች ሚኒስትር-  አቶ ላቀ አያሌው
  • የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር - ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ
  • የማዕድን ሚኒስትር- ኢ/ር ታከለ ኡማ
  • የፕላንና ልማት ሚኒስትር - ዶ/ር ፍጹም አሰፋ
  • የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር- ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ
  • የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር - አቶ ቀጄላ መርዳሳ ሆነዋል።

1 min read

Published

By Stringer Report


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now