ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ኦክቶበር 06 ያቀረቡት የካቢኔ አባላት ሹመቶች በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይሁንታን አግኝቷል።
በአብላጫ ድምፅ ይሁንታ የተቸራቸው ሾመቶች በድምፅ አሰጥታ ወቅት 2 ተቃውሞና 12 ድምፀ ተአቅቦ አግኝቷቸዋል።
በዚህም መሠረት፦
- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር - ደመቀ መኮንን
- መከላከያ ሚኒስትር - ዶ/ር አብረሃም በላይ
- የገንዘብ ሚኒስትር - አህመድ ሽዴ
- የሥራና ክህሎት ሚኒስትር - ሙፈሪሃት ካሚል
- ግብርና ሚኒስትር - ኡመር ሁሴን
- የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር - ኢ/ር አይሻ መሃመድ
- የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር - ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ
- የትምህርት ሚኒስትር - ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ
- የትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ሚኒስትር - ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ
- የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር- አቶ ገብረመስቀል ጫላ
- የኢንዱስትሪ ሚኒስትር- አቶ መላኩ አለበል
- የሰላም ሚኒስትር- አቶ ብናልፍ አንዷለም
- የፍትህ ሚኒስትር- ዶ/ር ጌዴዎን ጤሞጢዎስ
- የጤና ሚኒስትር- ዶ/ር ሊያ ታደሰ
- የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር- አቶ በለጠ ሞላ
- የቱሪዝም ሚኒስትር- አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ
- የገቢዎች ሚኒስትር- አቶ ላቀ አያሌው
- የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር - ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ
- የማዕድን ሚኒስትር- ኢ/ር ታከለ ኡማ
- የፕላንና ልማት ሚኒስትር - ዶ/ር ፍጹም አሰፋ
- የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር- ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ
- የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር - አቶ ቀጄላ መርዳሳ ሆነዋል።
Share

