የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣንን የቦርድ አባላት ሹመት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀደቀ።
የቦርዱ ዘጠኝ አባላት ለሹመት የበቁት በአብላጫ ድምፅ ሲሆን፤ 11 ተቃውሞና 17 ድምፀ ተአቅቦ ገጥሟቸዋል።
በዛሬው ዕለትም ቃለ መሐላ ፈፅመዋል።
የተሿሚዎች ዝርዝር፤
1. አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር – ሰብሳቢ
2. አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ ከቱሪዝም ሚኒስቴር – አባል
3. አምባሳደር ሐሰን አብዱልቃድር ከዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል – አባል
4. ዶክተር አጋረደች ጀማነህ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ – አባል
5. ዶክተር በድሉ ዋቅጅራ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ -አባል
6. ዶክተር መሣይ ገብረማርያም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ – አባል
7. ዶክተር ወዳጀነህ ማኅረነ አማካሪ – አባል
8. ቀሲስ ታጋይ ታደለ ከሃይማኖት ተቋማት – አባል
9. ኡስታዝ ያሲን ኑሩ ከሃይማኖት ተቋማት - አባል ሆነዋል።

