የተናጠል የተኩስ አቁም ውሳኔው "አሸባሪው ሕወሓት" እየፈጸመ ባለው ጥቃት የተነሳ የታለመለትን ዒላማ ሊያሳካ እንዳልቻለ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለፀ።
የተወሰደውን የተኩስ አቁም ውሳኔ ሃሳብ ለመለወጥ እያስገደደው እንደሆነም መንግስት አመልክቷል።
ሚኒስቴሩ ወቅታዊውን የኢትዮጵያ ሁኔታ አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል።
"ሕወሓት በከፈተው ጥቃት ከአፋርና አማራ ክልሎች ከ300 ሺህ በላይ ሰዎች እንዲፈናቀሉና በሺዎች የሚቆጠሩ ህይወታቸውን እንዲያጡ አድርጓል ፣ እየፈጸመ ያለውን ሰብዓዊ ግፍም የዓለም ዓቀፉ ማኅበረሰብ ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎታል" ብሏል መግለጫው።
በመሆኑም ተጨማሪ ጥፋትና ግፍ እንዲፈጸምና ዜጎች ኑሯቸው እንዲመሰቃቀል መንግስት የማይፈቅድ መሆኑን የጠቆመው መግለጫው ለሰብዓዊ ድጋፍ ሲባል የተወሰደውን የተኩስ አቁም ውሳኔ ሃሳብ ለመለወጥ እያስገደደው ነው ብሏል።
[ ደመቀ ከበደ ፡ አዲስ አበባ ]

