የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲታወጅ ጠየቀ

*** አብን አጥቂዎች በግልፅ ፍርድ እንዲበየንባቸው፤ ይህን ችላ ያሉ፣ እንዲባባሱ ያደረጉ ሚዲያዎች፣ ፓለቲከኞች እና ግለሰቦችን መንግስት ተጠያቂ እንዲያደርግና ብሔራዊ የሐዘን ቀን እንዲታወጅም ጠይቋል።

News

Dr Belete Molla (R). Source: AMC

ንቅናቄው በምዕራብ እና ምስራቅ ወለጋ በአማራ ብሔር ተወላጆች ላይ ተደጋጋሚ አሰቃቂ ጥቃት መፈፀሙን ረቡዕ ሰኔ 29 ባወጣው መግለጫ ገልጧል።

አብን "ይህ ጥቃት በአማራ ሕዝብ ላይ ሲፈፀም አዲስ አይደለም፤ ይልቁንስ የተሳሳተው ትርክት አንዱ ቅርንጫፍ ነው" ሲል አስታውቋል።

የንቅናቄው ሊቀመንበር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በበኩላቸው "አማራ ጠል ትርክት ከውጭም ከውስጥም ጠላት አፍርቶልናል እናም በዚህ ደግሞ እየተጎዳ ያለው ምስኪን ራሱን መከላከል የማይችል ሕዝብ ነው፤ የአሁኑን ጨምሮ ተከታታይ ችግሮችን ለማስቆም የሚመለከታቸው ሁሉ ሊያስቆሙት ይገባል" ሲሉ አሳስበዋል።

አክለውም "በአማራ ሕዝብ ላይ እየተደረገ ያለውን ዘር የማጥፋት ጥቃት የሚመለከታቸው ሁሉ ሊያስቆሙት ይገባል፤ ንቅናቄው በአማራ ሕዝብ ላይ አየተፈፀመ ያለው ስልታዊ ዘር ማጥፋት ነው ብሎ" ሲሉም ገልጠዋል። 

አብን፤ የአማራ ሕዝብ ተከታታይ ግድያ ግድ ሊለው የሚገባው የመንግስት መዋቅር ችላ ማለቱን እንዲያቆም እና ባስቸኳይ ሕዝብን እንዲጠብቅ በማለት ያሳሰበ ሲሆን፤ አያይዞም "ጥቃቱን እየተከታተለ እርምጃ ያልወሰደው መንግስት ይህንን ጥቃት እየሸፈኑ ያሉ እንዲሁም ሕዝብን መጠበቅ ያለባቸው ከክልል እስከ ፌደራል ቢሮዎች ተጠያቂ ናቸው" ሲልም አብን አስታውቋል።

አክሎም፤ ጥቃቱን ለማስቆም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲታወጅና የአካባቢው ነዋሪዎች በፀጥታ አካልነት ተካትተው ራሳቸውን እንዲጠብቁ የሚያስችል ሥራ እንዲሰራ አብን ጠይቋል።

አብን አጥቂዎች በግልፅ ፍርድ እንዲበየንባቸው፤ ይህን ችላ ያሉ፣ እንዲባባሱ ያደረጉ ሚዲያዎች፣ ፓለቲከኞች እና ግለሰቦችን መንግስት ተጠያቂ እንዲያደርግና ብሔራዊ የሐዘን ቀን እንዲታወጅም ጠይቋል።

ንቅናቄው "አማራ የመጣበትን ችግር ለመመከት እንደ ሕዝብ በአንድነት ለመመከት አንድነቱን ጠብቆ የመጣውን የዘር ማጥፋት ጥቃት ለመመከት እንዲሠራ' ሲል ጥሪ ያቀረበ ሲሆን፤ በመጪው ሐሙስ የሐዘን ቀንን ለማሰብ የሻማ ማብራት፣ የፓናል ውይይት እና ሌሎች ዝግጅትን ለማከናወን ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጧል።

ምንጭ AMC


Share

Published

Updated

By Stringer Report

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service