የደሴና ተንታ ግንባር ከተሞች ከሕወሓት እጅ ወጥትተው በመንግሥት ቁጥጥር ስር መሆናቸውን የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ባወጣው ወታደራዊ መግለጫ አስታወቀ።
በመግለጫው መሠረት የተእቀቁት ከተሞች፤
- በደሴ ግንባር ሐይቅ፣ ቢስቲማ፣ ባሶሚሌ እና ውጫሌ ከተሞች
- በተንታ ግንባር ዓለም አምባ፣ መቅደላና ጎሽሜዳ ናቸው።
በሌላም በኩል ከጦር ግንባር ወደ ቢሮ ሥራቸው ለጊዜው መመለሳቸውን ያስታወቁት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በወቅታዊው የኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ከኤርትራ፣ ኬንያ፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳንና ጂቡቲ መሪዎች ጋር ሰፋ ያለ የስልክ ውይይት ማድረጋቸውንና ምስጋናም ማቅረባቸውን ገልጠዋል።
በሕወሓት በኩል በሁለት ቀናት ውስጥ የሕወሓት ጦር 158 ኪሎ ሜትሮችን በእግር መጓዙንና በ10 ሺህ የሚቆጠር የመንግሥት ጦር ለሕልፈት ሕይወት መዳረጉን በቃል አቀባዩ በኩል የገለጠ ሲሆን፤ ሰሞኑን በቁጥጥሩ ስር ያደረጋቸው ወይም ከእጁ ወጥተው በመንግሥት ሠራዊት እጅ ስለገቡ ከተሞች አላነሳም።

