የኢትዮጵያ መንግሥት የተናጠል ተኩስ አቁሙን ማንሳቱን አስታወቀ

*** መንግሥት ባወጣው መግለጫ ለአገር መከላከያ ሠራዊት፣ የክልል ልዩ ኃይሎችና ሚሊሻዎች አቅጣጫ ማስቀመጡን ገልጧል።

Abiy Ahmed, Ethiopia's prime minister.

Abiy Ahmed, Prime Minister of Ethiopia. Source: Getty

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ዛሬ ነሐሴ 4 2013 ባወጣው መግለጫ ቀደም ሲል ወስዶት የነበረውን የተናጠል ተኩስ አቁም እርምጃ ማብቃቱን አስታወቀ።

መንግሥት በመግለጫው የአገር መከላከያ ሠራዊታችን፣ የክልል ልዩ ኃይሎችና ሚሊሻዎች፤ የኃይል እርምጃ መውሰድ እንዲችሉ አቅጣጫ የተቀመጠላቸው መሆኑን ገልጧል። ለተለያዩ የማሕበረሰብ አባላትም ከሠራዊቱ ጎን እንዲቆሙ ጥሪ አስተላልፏል። 

አያይዞም "ውጊያው የትግራይን ሕዝብ ምሽግ ካደረገው እኩይ ኃይል ጋር እንጂ ከትግራይ ጋር አይደለም" ብሏል።  

በሕወሓት በኩል ለጊዜው የተሰጠ የአጸፋ መግለጫ ባይኖርም ዘግይቶም ቢሆን የአቋም መግለጫ ያወጣል ተብሎ ይጠበቃል። 


1 min read

Published

By Stringer Report


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now