በውጫሌና ሌሎች ግንባሮች ተጨማሪ ከተሞች ተለቀቁ

*** "ጋሸናና ኣምባሰል ዛሬ ስለሆነውና ስለሚቀጥለው ሌላ ጊዜ እንመለሳለን" የሕወሓት ቃል አቀባይ ጌታቸው ረዳ

Homeland Report

Source: SBS Amharic

የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ማምሻውን እንዳስታወቀው በምሥራቅና ውጫሌ ግንባሮች ቀደም ሲል በሕወሓት ቁጥጥር ስር የነበሩ ከተሞች በመንግሥት ቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቋል።

በዚህም መሠረት፤

  • በምሥራቅ ግንባር የዞብል ሰንሰለታማ ተራሮችን ጨምሮ የአርጆ፣ ፎኪሳ እና ቦረን ከተሞች 
  • የጉራ ወርቄ አካባቢዎችን በመቆጣጠር የወልድያ መቀሌ ዋናውን አውራ ጎዳና በመቁረጥ የድሬ ሮቃና የሶዶማ ከተሞች
  • በውጫሌ ግንባር የአምባሰል ከፍተኛ ሰንሰለታማ ተራሮችን ጨምሮ የሮቢትና የጎልቦን፣ በወረባቦ ወረዳ የሚሌ ኮትቻን፣ በሐብሩ ወረዳ የኮልቦን፣ የመርካታና የፋጂን አካባቢዎች በመንግሥት ቁጥጥር ስር ውለዋል። 

በሌላ በኩል የሕወሓት ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ በመንግሥት በኩል የህወሓት ጦር "የቆቦ ወልድያ መንገድ ስለተዘጋበት በጋሸናና ላሊበላ" በኩል ሰብሮ ለመውጣት ሙከራ ስለማድረጉ የተገለጠውን ሲያስተባብሉ "ጋሸናና ኣምባሰል ዛሬ ስለሆነውና ስለሚቀጥለው ሌላ ጊዜ እንመለሳለን" የሚል ምላሽ ሰጥተዋል። 

 


1 min read

Published

By Stringer Report


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now