የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ወደ አፍሪካ ሊጓዙ ነው

*** አንቶኒ ብሊንከን በአምስት ቀናት የአፍሪካ ቆይታቸው ወደ ኢትዮጵያ አይዘልቁም

Homeland Report

U.S. Secretary of State Antony Blinken. Source: Getty

አንቶኒ ብሊንከን ከኖቬምበር 15 እስከ 20 ባሉት ቀናት ከሶስት የአፍሪካ አገራት ጋር ሊመክሩ ነው

ሚኒስትሩ ጉዟቸውን ወደ ኬንያ፣ ናይጄሪያና ሴኔጋል እንደሚያደርጉ ሚኒስቴር መስሪያ ቤታቸው አስታውቋል።

የአሜሪካው ከፍተኛ ዲፕሎማት በናይሮቢ ቆይታቸው ከፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ጋር ይመክራሉ።

ኢትዮጵያ፣ ሶማሊያና ሱዳንን የተመለከቱ አካባቢያዊና የፀጥታ ጉዳዮችን እንዲሁም ኮቪድ 19 የመሪዎቹ ግንኙነት ማጠንጠኛ ሃሳቦች መሆናቸውን የብሊንከን መስሪያ ቤት ገልጿል።

በቀጣይም ብሊንከን አቡጃ ደርሰው ከናይጄሪያው ፕሬዚዳንት ሙሃመድ ቡሃሪ ጋር ከዛም በሴኔጋል ዳካር ላይ ፕሬዝዳንት ማኪ ሳልን አግኝተው ወደ ሃገራቸው ይመለሳሉ።


1 min read

Published

By Stringer Report


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now