የዩናይትድ ስቴትስ የምሥራቅ አፍሪካ ልዩ ልዑክ ከኃላፊነታቸው እንደሚለቁ እየተነገረ ነው

*** በጊዜያዊነት በምክትል ልዩ ልዑክ ፓይተን ኖፍ ሳይተኩ አይቀርም፤ ሁለቱም ልዑካን ዛሬ ኢትዮጵያ ይገባሉ።

News

David Satterfield, U.S. Special Envoy for the Horn of Africa. Source: Getty

የዩናይትድ ስቴትስ የምሥራቅ አፍሪካ ልዩ ልዑክ ዴቪድ ሳተርፊልድ እና ምክትል ልዩ ልዑክ ፓይተን ኖፍ ዛሬ ኤፕሪል 13 አዲስ አበባ ይገባሉ።

ልዑካኑ ከኢትዮጵያ የመንግሥት ባለስልጣናት፣ የረድኤት ድርጅቶች ተወካዮችና የዲፕሎማሲ ሽርካዎች ጋር ተገናኝተው ይነጋገራሉ። 

የጉብኝታቸው ተልዕኮም ዩናይትድ ስቴትስ ግጭቶች እንዲገቱ ፣ ገደብ አልባ የሰብዓዊ እርዳታ ተደራሽነት እንዲኖር፣ በሁሉም ተዋናዮች ዘንድ ግልፅነተ የተመላበት የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ምርመራዎች እንዲካሔዱና ኢትዮጵያ ላለው ግጭት በድርድር ዕልባት ለማበጀት በምታደርጋቸውን ጥረቶች መቀጠል እንደሆነ በአዲስ አበባ የአሜሪካ ኤምባሲ አስታውቋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ በወርኃ ጃኑዋሪ የዩናይትድ ስቴትስ ልዩ ልዑክ ሆነው የተመደቡት የቀድሞው በቱርክና ሊባኖስ የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር ዴቪድ ሳተርፊልድ ለጊዜው ይህ ነው ባልተባለ ይፋዊ ምክንያት የሥራ ኃላፊነታቸው እንደሚለቁ ፎሪን ፖሊሲ መፅሔት ዲፕሎማሲያዊ ምንጮን ጠቅሶ ገልጧል።  

በምትካቸውም በጊዜያዊነት ምክትላቸው ፓይተን ኖፍ በተጠባባቂነት የሥራ ኃላፊነቱን ተቀብለው እንደሚቀጥሉ ተጠቁማል። 


1 min read

Published

Updated

By Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now