የትግርኛ ሙዚቃ ተጫዋቹ አርቲስት ዳዊት ነጋ ከዚህ ዓለም በሞት ከመለየቱ በፊት ባደረበት ሕመም በሆስፒታል ሲረዳ ቆይቷል።
በ 34 ዓመቱ እንዳረፈ የተገለፀው ድምፃዊው ውልደትና ዕድገቱ መቀሌ እደማርያም ሰፈር ነው።
በልጅነቱ ሙዚቃ የጀመረው ዳዊት በተለይም "ባባ ኢለን" በተባለው ዘፈኑ ቋንቋውን በማይናገሩት ጭምር ከህዝብ ጋር በስፋት ተዋውቋል።
ዳዊት ነጋ ዘዊደሮ፣ ወዛመይ፣ ቸኮላታ፣ ኣጆኺ ትግራይ፣ ደስ ይበለኒ'ሎ፣ ቕዱስ ፀባያ የተሰኙ ዘፈኖቹ ከፍተኛ ተደማጭነት አግኝተውለት ነበር።
Share

