ኢሰመኮ የታሰሩበት የማይታወቁ ጋዜጠኞች ጉዳይ እንዳሳሰበው ገለጸ

*** ኢሰመኮ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የሰብዓዊ መብቶችን መርሆች ባከበረ መልኩ መተግበሩን የሚመለከታቸው አካላት በቅርብ ሊከታተሉ እና ሊያረጋግጡ እንደሚገባም ጥሪ አቅርቧል፡፡

Dr Daniel Bekele, Chief Commissioner of Ethiopian Human Rights Cpmmission.

Dr Daniel Bekele, Chief Commissioner of Ethiopian Human Rights Cpmmission. Source: EHRC

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ትናንት ባወጣው መግለጫ በእስር ላይ የሚገኙት ታምራት ነገራ፣ ክብሮም ወርቁ፣ መዓዛ መሃመድ እና የእያስፔድ ተስፋዬን ጉዳይ ለማጣራት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተነጋገረ መሆኑን የገለጸ ሲሆን በተለይም ታምራት ነገራ በፖሊስ ከተያዘበት ከታኅሣሥ 1 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ ያለበት ቦታ አለመታወቁ እንዳሳሰበው አስታውቋል፡፡

ኮሚሽኑ አክሎም ከጥቅምት 16 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ በእስር የቆየው ክብሮም ወርቁ በኅዳር 9 ቀን 2014 ዓ.ም. በፍርድ ቤት የዋስትና መብት ከተፈቀደለት ጊዜ ጀምሮ ኢሰመኮ ይህን መግለጫ እስካወጣበት ጊዜ ድረስ የተያበበት ቦታ ለቤተሰቦቻቸው አልተነገረም ብሏል፡፡

በዚህም ምክንያት የታሰሩ ጋዜጠኞች የቤተሰብ ጥየቃ መብታቸው ያልተከበረላቸው ከመሆኑም በላይ ያሉበት ሁኔታ አለመታወቁ ኮሚሽኑን እንዳሳሰበውና በአስቸኳይ ግዜ ሁኔታ ውስጥ ቢሆንም ታሳሪዎች ያሉበት ሁኔታ ሊታወቅና በቤተሰብ እና በሕግ አማካሪ የመጎብኘት መብቶች ሊጣሱ አይገባም ብሏል፡፡

በመሆኑም የሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት ሁለቱም ታሳሪዎች የሚገኙበትን ቦታ በአስቸኳይ ለቤተሰቦቻቸው እና ለሕግ አማካሪያቸው እንዲያሳውቁና በቤተሰቦቻቸው የመጎብኘት መብታቸውን እንዲያረጋግጡ ኢሰመኮ አሳስቧል፡፡

አያይዞም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የሰብአዊ መብቶችን መርሆች ባከበረ መልኩ መተግበሩን የሚመለከታቸው አካላት በቅርብ ሊከታተሉ እና ሊያረጋግጡ እንደሚገባም ጥሪ አቅርቧል፡፡


1 min read

Published

By Stringer Report


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now