አዲሱ የሶማሌ ክልል ምክር ቤት እያካሄደ ባለው የመጀመሪያ አመት ጉባኤው ላይ አቶ ሙስጠፋ ሙሀመድ ኡመርን የሶማሊ ክልል ፕሬዝዳንት አድርጎ መርጧል።
አቶ ሙስጠፋ በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት አማካኝነት የቃለ መሐላ ሥነ ስር ዓቱን ካጠናቀቁ በኋላ የክልሉ የመንግሥት ምሥረታ የሴቶችን ኮታና ተጠቃሚነት እንደሚያረጋግጥ፣ የሚሰየሙት የሥራ አስፈፃሚ አባላትም በትምህርት ዝግጅታቸውና የሥራ ልምዳቸው ብቁ የሆኑ እንደሚሆኑ ተናግረዋል።
አቶ ሙስጠፋ ሙሁመድ ባለፉት 3 አመታት የሶማሊ ክልልን በፕሬዚደንትነት መምራታቸው ይታወሳል።
Share

