ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ዛሬ እሑድ የካቲት 13 2014 የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ጀመረ።
የሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጨት ሥራ በይፋ መጀመርን ያስታውቁት በሥነ ሥርዓቱ ላይ ከከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር በስፍራው የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ናቸው።
ዛሬ ሥራ ላይ በዋለው አንድ ተርባይን አማካይነት መመንጨት የጀመረው ኃይል 375 ሜጋ ዋት ሲሆን የሕዳሴ ግድብ 13 ተርባይኖችን የያዘ ነው።
ግድቡ በሁለተኛ ዙር ሙሌቱ 13 ቢሊየን ኪዩቢክ ውኃ ያቋረ ሲሆን፤ የግንባታ ወጪው በተለያዩ አስባቦች ከታሰበለት 80 ቢሊየን ብር አልፎ 163 ቢሊየን ብር ደርሷል።
በሥነ ሥር ዓቱ ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የኃይል ምንጭ ጅማሮውን አስመልክተው "ዛሬ ለኢትዮጵያ የብርሃን መባቻ ነው" ብለዋል።
የግድቡ ሓይል ምንጭ ጅማሮ ለአካባቢው አገራትም ጭ ምር "ብሥራት" መሆኑን ተናግረዋል።
ለፕሮጄክቱ እውንነት ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ጀመሮ በተከታታይ የበኩላቸውን አስተዋፅዖ ያበረከቱ ቀደምት የኢትዮጵያ መሪዎችንም በስም ጠቅሰው አመስግነዋል።
ኢትዮጵያ ለጎረቤት አገራት እስከ ሁለት ሺህ ሜጋ ዋት ኃይል በመሸጥ 580 ሚሊየን ዶላርስ ያህል ዓመታዊ ገቢ ልታገኝበትም እንደምትችል ተነግሯል።

