የኢትዮጵያ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ዕለተ ሰኞ የካቲት 14 - 2014 ባካሔደው ልዩ ስብሰባ የ11 አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮችን ሹመት ማፅደቁን ይፋ አደረገ፡፡
ምክር ቤቱ ቀደም ሲል ጥር 27 - 2014 የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዕጩ ኮሚሽነሮች ላይ ሕብረተሰቡ አስተያየት እንዲሰጥባቸው የ42 ዕጩ ኮሚሽነሮችን ስም ዝርዝር፣ የትምህርት ደረጃና የሥራ ልምዶችን አካትቶ አቅርቦ ነበር።
በዛሬው ዕለት ምክር ቤቱ ሰብሳቢና ምክትል ሰብሳቢን አካትቶ ለ11 አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮች ይሁንታውን ቸሯል።
ኮሚሽነሮቹም በጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት መዓዛ አሸናፊ አማካይነት ቃለ መሐላ ፈፅመዋል።
1. ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ – ሰብሳቢ
2. ወይዘሮ ሂሩት ገብረስላሴ – ምክትል ሰብሳቢ
3. ዶክተር ተገኘወርቅ ጌቱ
4. አምባሳደር ዶክተር አይሮሪት መሃመድ
5. ወይዘሮ ብሌን ገብረመድህን
6. ዶክተር ዮናስ አዳዬ
7. አቶ ዘገየ አስፋው
8. አቶ መላኩ ወልደማሪያም
9. አምባሳደር መሐሙድ ድሪር
10. አቶ ሙሉጌታ አጎ እና
11. ዶክተር አምባዬ ኦጋቶ ናቸው።

