በ734 ሚሊዮን ብር የተከፈለና በ2.9 ቢሊዮን ብር የተፈረመ ካፒታል የተቋቋመዉ ፀሐይ ባንክ አ.ማ 30 ቅርንጫፎችን በመክፈት በይፋ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ

*** የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዢ ዶ/ር ይናገር ደሴ ከባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አመራሮችና የአክሲዮን ማኅበሩ ባለቤቶች ጋር በመሆን በቅሎ ቤት አካባቢ የተከፈተዉን የፀሐይ ባንክ ቅርንጫፍ በመመረቅ አገልግሎቱን በይፋ አስጀምረዋል።

News

Source: Tsehay

የፀሐይ ባንክ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ያሬድ መስፈን ባንኩ 30 ቅርንጫፎችን በመክፈት አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በመግለጽ በቅርቡ የቅንጫፎቹን ብዛት ወደ 50 ያሳድጋል ብለዋል።

የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ታዬ ዲበኩሉ ባንኩ በ373 ባለአክሲዮኖች: በ734 ሚሊዮን ብር የተከፈለና በ2.9 ቢሊዮን ብር የተፈረመ ካፒታል ተቋቁሞ ስራ መጀመሩን አስታዉቀዋል።

የብሔራዊ ባንክ ገዢዉ ዶ/ር ይናገር ደሴ ከለዉጡ ወዲህ በርካታ ባንኮች እየተቋቋሙ መሆናቸዉን በመግለጽ በሃገሪቱ ያሉት ባንኩች ቁጥር 30 የማይክሮ ፋይናንሶች ብዛት ደግሞ 40 መድረሱን ተናግረዋል።

ባንኮቹ የገጠሩንና የከተማዉን ማህበረሰብ ኑሮ ከማሻሻል ረገድ ትልቅ ድርሻ ይኖራቸዋል ብለዋል።

ፀሐይ ባንክ በቴክኖሎጂ ዘመን የተቋቋመ ባንክ እንደመሆኑ መጠን የተሻለ የባንክ አገልግሎት ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል።

ፀሐይ ባንክን ጨምሮ በሃገሪቱ ዉስጥ ያሉ ባንኮችን አቅም ለማሳደግ ብሄራዊ ባንክ ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።

ባንኩ ምረቃዉን ምክንያት በማድረግና ማህበራዊ ሃላፊነቱን ለመወጣት ለጌርጌሴኖን የመረዳጃ ማህበር 300 ሺህ ብር : ኒያ ፋዉንዴሽን ጆ ኦቲዝም 300 መቶ ሺህ ብር: ለኩላሊት የበጎ አድራጎት ድርጅት 500 ሺህ ብር: ለኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ ማዕከል የ500 ሺህ ብር የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል።


Share

Published

By Stringer Report

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service