ኢትዮ ቴሌኮም በ2014 በጀት ዓመት 61 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን ገለጠ

*** የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞች ብዛት 66 ነጥብ 59 ሚሊዮን ደርሷል።

News

Frehiwot Tamru, Chief Executive Officer of Ethio Telecom Source: EthTelecom

ዛሬ ማለዳ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ የ2014 የበጀት ዓመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት አስመልክቶ ለጋዜጠኞች ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ፍሬሕይወት ታምሩ በበጀት ዓመቱ 70 ቢልዮን ብር ለማግኘት ታቅዶ እንደነበር ያነሱት ዋና ስራ አስፈጻሚዋ የእቅዱን 87 ነጥብ 6 በመቶ ማሳካት ተችሏል ብለዋል።

እንደ ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ገለፃ የውጭ ምንዛሪ ከሚያስገኙ አገልግሎቶችም ከ146 ሚልዮን ዶላር በላይ ተገኝቷል

ኢትዮ-ቴሌኮም የአገልግሎት ተጠቃሚን ቁጥር ለማሳደግ ከታቀደው እቅድ 104 በመቶ ማሳካቱን ዋና ስራ አስፈፃሚ ገልፀዋል።

ዋና ስራ አስፈጻሚዋ እንዳሉት የአገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞች ብዛት 66 ነጥብ 59 ሚሊዮን መድረሱን ገልጸው የበጀት ዓመቱ አፈጻጸም ከባለፍው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ18 ነጥብ 4 በመቶ እድገት አሳይቷል ብለዋል።

በሰሜን ኢትዮጵያ የተፈጠረውን ጦርነት ጨምሮ ሌሎች በሀገሪቱ የተስተዋሉ አለመረጋጋቶች ለቴሌኮም መሰረተ ልማት መውደም እና ለእቅዱ አለመሳካት ዋነኛ ምክንያት መሆናቸውንም ጠቅሰዋል።

[ደመቀ ከበደ ፡ አዲስ አበባ]


Share

Published

By Demeke Kebede

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service