የኢትዮጵያ መንግሥት የሰላም ተደራዳሪ ቡድን ሰየመ

*** የሰላም ተደራዳሪው ቡድን ሰብሳቢ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ናቸው

News

Demeke Mekonne, Deputy Prime Minster and Foreign Minster of Ethiopia. Source: Getty

የኢፌዴሪ መንግሥት በሰሜን ኢትዮጵያ ተክስቶ ላለው የሰላም መደፍረስ ሰላማዊ መፍትሔ ለማስገኘት እንዲያስችል አንድ ተደራዳሪ ቡድን ሰይሟል።

ሰባት አባላት ያሉት የተደራዳሪ ቡድኑ በገዢው ብልፅግና ፓርቲ ስራ አሥፈፃሚና ማዕከላዊ ኮሚቴ አማካይነት ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓትን በሚያስጠብቅና ብሔራዊ ጥቅምን በሚያስከብር ማዕቀፍ ውስጥ እንዲደራደር የውክልና ኃላፊነት የተሰጠው መሆኑ ተገልጧል።

የሰላም ተደራዳሪ ቡድን ሰብሳቢና አባላት ዝርዝርም በጠቅላይ ዐቃቤ ሕግና የብልፅግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ አማካይነት ሰኞ ሰኔ 20 / 2014 ይፋ ተደርጓል።

በዚህም መሠረት፤

  • አቶ ደመቀ መኮንን ሰብሳቢ
  • ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ አባል
  • አቶ ተመስገን ጥሩነህ አባል
  • አምባሳደር ሐሰን አብዱልቃድር አባል
  • አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን አባል
  • ሌተና ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ አባል
  • ዶ/ር ጌታቸው ጀምበር አባል ሆነው ተመድበዋል።     

1 min read

Published

By Stringer Report


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now