ከጠቅላይ ዐቃቤ ሕግነታቸው በመነሳት ከነሐሴ 12 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ የኢንጂነር ታከለ ኡማ የማዕድን እና ነዳጅ ሚኒስትር በመሆን መሾማቸውን ተከትሎ ወ/ሮ አዳነች የአዲስ አበባ ከተማን በምክትል ከንቲባነት ሲመሩ ቆይተዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው ጉባዔ የባሕል እና ቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ የነበሩትን ቡዜና አልቃድርን አፈጉባዔ አድርጓል፡፡
አዲስ የተሾሙት ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤም ዛሬ ቃለ መሃላ ፈጽመዋል፡፡
ወይዘሮ አዳነች አቤቤ የአዳማ ከተማ ከንቲባ፣ የገቢዎች ሚኒስትር እና የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ በመሆን ማገልገላቸው ይታወሳል፡፡
[ ደመቀ ከበደ ፣ አዲስ አበባ ]
Share

