ቴዲ አፍሮ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ቅዳሜ ሊሰጠው ነው
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ዶክተር አስራት አፀደወይን ለSBS አማርኛ እንደገለፁት ለድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) የክብር ዶክትሬት እንዲሰጠው የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ዛሬ ወስኗል ብለዋል።
በዚህም ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ቅዳሜ ሐምሌ 24/2013 ዓ.ም በተማሪዎች ምረቃ ዕለት ተገኝቶ የክብር ዶክትሬቱን እንደሚቀበል የገለፁት ዶክተር አስራት ዩኒቨርሲቲያችን ለዚህ የአገር ባለውለታና " ፍቅር ያሸንፋል" ለሚለው መርሁ ተገቢውን ክብርና እውቅና በመስጠቱ ታላቅ ደስታ ይሰማናል ብለዋል።
ለድምፃዊ፣ የዜማና ግጥም ደራሲው ቴዲ አፍሮ ላበረከተው ሙያዊ አስተዋፅኦ የክብር ዶክትሬት ዕውቅና ሊሰጠው መሆኑን በተመለከተ መረጃው ይፋ ከተደረገበት ቅፅበት አንስቶ አድናቂዎቹ በሶሻል ሚዲያ ደስታቸውን እየገለፁ ነው።
[ ደመቀ ከበደ ፣ አዲስ አበባ ]

