የተከዜ ድልድይ ፈረሰ

*** የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ የተከዜ ድልድይ መሰበር "በእጅጉ አሳስቦኛል" ብሏል።

Tekeze Bridge.

Tekeze Bridge. Source: EPA

የተከዜ ድልድይ መፍረሱን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ ገለጠ።

የመረጃ ማጣሪያው "የትግራይ አርሶ አደሮች  የግብርና ሥራቸውን እዲያከናውኑ ለመደገፍ የወጣውን የሰብዓዊ የተኩስ አቁም ስምምነቱን ውድቅ ያደረገው የሽብር ቡድኑ ሕወሓት የተከዜ ድልድይን ሆን ብሎ" አፍርሷል ብሏል።

በሕወሓት በኩል እስካሁን ይፋ ማስተባበያም ሆነ ማረጋገጫ አልተሰጠም።

የተከዜ ድልድይ እንዳባጉናና ማይፀምሪን የሚያገናኝ ነው። 

የድልድዩን መሰበር እውነታነት አስመልክቶ የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ የደቡባዊና ምሥራቃዊ አፍሪካ ቢሮ የገለጠ ሲሆን፤ አያይዞም ሰብዓዊ እርዳታውን በእጅጉ አስከፊ የሞት ሽረት ሁኔታ ለሚገኙ ሰዎች ላይ የሚያሳድረው ተፅዕኖ በእጅጉ ያሳሳበው መሆኑን አስታውቋል።

OCHA
Source: OCHA

የኢትዮጵያ መንግሥት ሰኞ ጁን 28 የተናጠል ተኩስ ማቆም እወጃ ማድረጉ ይታወሳል። 

 

 


1 min read

Published

Updated

By Stringer Report


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now