የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ አቃቤ ህግ በተለያዩ ወንጀሎች የጠረጠራቸውን የ39 ግለሰቦች ያለመከሰስ መብት እንዲነሳ ያቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ በሙሉ ድምጽ አፀደቀ።
በዚህም መሰረት፦
ዶክተር ደብረጸዮን ገብረሚካኤል
አቶ አስመላሽ ወልደስላሴ
አቶ አባይ ፀሃዬ
ዶክተር አምባሳደር አዲስ ዓለም ቤሌማ
አቶ ጌታቸው ረዳ
አቶ አፅበሃ አረጋዊ
አቶ ገብር እግዚአብሄር አርአያ እና ሌሎችም የህወሓት ተወካዮች ላይ የቀረበው ያለመከሰስ መብት የውሳኔ ሀሳብ በሙሉ ድምጽ ፀድቋል።
ግለሰቦቹ የተጠረጠሩበት ወንጀሎችም ጦር መሳሪያ ይዞ በማመፅ፣ የሀገር መከላከያን በመውጋት እና በሌሎችም ተያያዥ ወንጀሎች ዋና አድራጊነት ነው መሆኑ ታውቋል።
ኤፍ.ቢ.ሲ
Share

