ጠቅላይ አቃቤ ሕግ በወንጀል የጠረጠራቸው የ39 ግለሰቦች ያለመከሰስ መብት ተነሳ

*** የተጠርጣሪዎቹ ያለ መከሰስ መብት እንዲነሳ በሙሉ ድምፅ ያጸደቀው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነው

General Attorney

Source: Pexels

የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ አቃቤ ህግ በተለያዩ ወንጀሎች የጠረጠራቸውን የ39 ግለሰቦች ያለመከሰስ መብት እንዲነሳ ያቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ በሙሉ ድምጽ አፀደቀ።

በዚህም መሰረት፦

ዶክተር ደብረጸዮን ገብረሚካኤል

አቶ አስመላሽ ወልደስላሴ

አቶ አባይ ፀሃዬ

ዶክተር አምባሳደር አዲስ ዓለም ቤሌማ

አቶ ጌታቸው ረዳ

አቶ አፅበሃ አረጋዊ

አቶ ገብር እግዚአብሄር አርአያ እና ሌሎችም የህወሓት ተወካዮች ላይ የቀረበው ያለመከሰስ መብት የውሳኔ ሀሳብ በሙሉ ድምጽ ፀድቋል።

ግለሰቦቹ የተጠረጠሩበት ወንጀሎችም  ጦር መሳሪያ ይዞ በማመፅ፣ የሀገር መከላከያን በመውጋት እና በሌሎችም ተያያዥ ወንጀሎች ዋና አድራጊነት ነው መሆኑ ታውቋል።

ኤፍ.ቢ.ሲ


1 min read

Published

Updated

By Stringer


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now