ብሪስበን የ2032 የኦሎምፒክና ፓራኦሎምፒክ አስተናጋጅ ከተማ ሆና በዓለም አቀፍ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ተመረጠች።
የብሪስበን የኦሎምፒክ አስተናጋጅ ሆኖ መመረጥ አውስትራሊያን ቀደም ሲል ኦሎምፒክን በሶስት ከተሞች ካስተናገደችው ዩናይትድ ስቴትስ ጎን አሰልፏታል።
አውስትራሊያ ቀደም ሲል ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፈችበትን ኦሎምፒክ ባዘጋጀችው ሜልበርንና ሲድኒ ከተሞች የበጋ ኦሎምፒኮችን አስተናግዳለች።

በዛሬው ዕለት የኩዊንስላንድ ፕሪሚየር አናስታዥያ ፓለሼይ እና የአውስትራሊያ ልዑካን ቡድን አባላት ለዓለም አቀፍ ኦሎምፒክ ኮሚቴ የመጨረሻ የብሪስበንን ምረጡ ዝግጅታቸውን አቅርበዋል።

የዓለም አቀፉን ኦሎምፒክ ኮሚቴ ውሳኔ በጉጉት በቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት ሲጠባበቁ የነበሩ የብሪስበን ነዋሪዎችም ደስታቸውን ገልጠዋል። ርችትም ተተኩሷል።


