ከተማም እንደ ሰው

ሥነ ግጥም

Kebedech's poem

New York Source: AAP

ሲከፋው፤

ከተማም እንደ ሰው ልጅ መልክ

የታመቀ ህመም ግርዶሽ

በበሩ ድባብ ይጥላል

የተነከረ ከል ሸማ

የጠቆረ ማቅ ይለብሳል

ፅልመት ፀሐዩን ያደምቃል

ሲቃጠል ብርሃን አይሰጥም

ሲጋይ ሙቀት አይወልድም

እንደ በረዶ ክምር

አጥንት ያቀዘቅዛል

የደም ዝውውር አግዶ

የስትንፋስ ሂደት ይዘጋል

አንድ ባንድ የተካበው ካብ

በቅፅበት ግፊት ተንዶ

በበቀል ክብሪት ይጫራል።

ያልተቀመረ ብሶት ጎርፍ

አይኑን ጨፍኖ ይንዳል

የጊዜን ምልክት ሳያይ

የዘመኑን ስልት ሳያጤን

የመፍትሄ ክር ይበጥሳል።

ሃሳብን ከሰው የማይለይ

በእስትንፋስ የማይፀገይ

ችግኝ ይኮተኩታል።

ከበደች ተክለአብ

እንደ አውሮጳ አቆጣጠር ጁላይ 2020

*ይህ ግጥም ቀደም ሲል በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ ለሕትመት በቅቷል።


1 min read

Published



Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now