የቀድሞዋ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤና የሕወሓት ሥራ አስፈጻሚ አባል ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም በዋስ ተለቀቁ፡፡
በሌላም በኩል፤ በእነ አቶ ስብሀት ነጋ የክስ መዝገብ ተጠርጥረው ክስ ተመስርቶባቸው የነበሩት የትግራይ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት የነበሩትን ወ/ሮ ሕርቲ ምህረተአብና የትግራይ ክልል መንግሥት አማካሪ የነበሩት ወልደ ጊዮርጊስ ደስታ፣ በእነ አቶ ዓባይ ወልዱ የክስ መዝገብ ተከሳሽ የነበሩት አምደማርያም ተፈራ እያንዳንዳቸው በ30 ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቁ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ወስኗል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞም ወ/ሮ ሙሉ ገብረ እግዚአብሔር በወንጀል ተፋላጊ መሆናቸው ተጠቅሶ ማረሚያ ቤት እንዲቆዩ የፍርድ ቤት ተዕዛዝ ተላልፎባቸዋል።
አቶ ስብሐት ነጋን አክሎ አቶ ሰሎሞን ኪዳኔ ቅዱሳን ነጋና ሌሎች ተጠርጣሪዎች ጉዳያቸው በቀዳሚ ምርመራ እንዲታይ ዐቃቤ ሕግ ጉዳዩን ላስቻለው ፍርድ ቤቱ አመልክቷል።
በአቤቱታውም መሠረት፤ አቶ ስብሐት ነጋን ጨምሮ የመዝገቡ ተጠርጣሪዎች ጉዳያቸው በቀዳሚ ምርመራ መዝገብ እስከሚታይ በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ አስተላልፏል።

