የሌበር ሲናተር ኪምበርሊ ኪቺንግ ማምሻውን በድንገት ሕይወታቸው አለፈ

*** የሴናተሯን ድንገተኛ ሕልፈተ ሕይወት ተከትሎ ከሥራ ባልደረቦቻቸው፣ ወዳጆቻቸውና ዜጎች የጥልቅ ሐዘን መልዕክቶች እየጎረፉ ነው።

Senadora Kinberley Kitching morre aos 52 anos

Senadora Kinberley Kitching morre aos 52 anos Source: AAP

የሌበር ሴናተር ኪምበርሊ ኪችንግ በ52 ዓመታቸው በድንገት ሜልበርን ውስጥ ለሕልፈተ ሕይወት ተዳርገዋል።

የሞታቸው አስባብም የልብ ድካም ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል። 

ሕልፈተ ሕይወታቸውን ተከትሎ ከሥራ ባልደረቦቻቸውና ወዳጆቻቸው የሐዘን መግለጫ መልዕክቶች በማኅበራዊ ሚዲያ በኩል እየጎረፉ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰንም "በዜና ዕረፍታቸው ጥልቅ ሐዘን" እንደተሰማቸው ገልጠዋል።

News
Source: S.Morrison

የቀድሞው ሌበር መሪ ቢል ሾርተን ሴናተር ኪቺንግ ዛሬ ሐሙስ ምሽት "በልብ ሕመም ተሰቃይተው" እምብዛም ሳይቆዩ ሕይወታቸው እንዳለፈ ገልጠዋል።

የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘንጋር አያይዘውም "የሳቸው ህልፈት ለሌበርና ለአገር ትልቅ እጦት ነው" ብለዋል። 

የተቃዋሚ ቡድን ሌበር መሪ አንቶኒ አልባኒዚም በበኩላቸው የተሰማቸውንን ሐዘንና በሴናተር ኪምበርሊ ኪቺንግ ድንገተኛ ሞት የሌበር ቤተሰብ የተደናገጠ መሆኑን በቲዊተር ገፃቸው አስፍረዋል።    

News
Source: A.Albanese.

ሴናተር ኪቺንግ የተወለዱት በ1970 ብሪሰበን ከተማ ሲሆን ከ2001 እስከ 2004 የሜልበርን ማዘጋጃ ቤት ተመራጭ ሆነው አገልግለዋል።  

የጤና ሠራተኞች ማኅበር ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው ሠርተዋል። 

ከሶስት አሠርት ዓመት በላይ የሌበር ፓርቲ አባል የነበሩ ሲሆን በ2016 የሌበር ሴናተር ሆነዋል።

የፓርላማ የውጭ ጉዳዮች፣ መከላከያና ንግድ ኮሚቴ ምክትልና ዋና ሰብሳቢ ሆነው መርተዋል።  

 


1 min read

Published

By NACA

Presented by Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now