የሌበር ፓርቲ ዛሬ ቅዳሜ ማርች 19 የተካሔደውን የደቡብ አውስትራሊያ ምርጫ አሸንፏል።
የፓርቲው መሪ ፒተር ማሊናዩስካስ 47ኛው የደቡብ አውስትራሊያ ፕሪሚየር ለመሆን በቅተዋል።
የፌዴራል ሌበር መሪ አንቶኒ አልባኒዚ ለአዲሱ ተመራጭ ፕሪሚየር ማሊናዩስካስ የእንኳን ደስ ያለዎት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ሌበር ፓርቲ የአያሌ መራጮችን ድምፅ ማግኘት በመቻሉ 27 የምክር ቤቶችን አሸንፏል።
የሊብራል ፓርቲ 15 የምክር ቤት ወንበሮችን ያገኘ ሲሆን የግል የምክር ቤት ተወዳዳሪዎች ስድስት ወንበሮችን ለማሸነፍ ችለዋል።
ሌበር ፓርቲ ራሱን ችሎ መንግሥት ለማቆም ማሸነፍ ይጠበቅበት የነበረው 24 የምክር ቤት ወንበሮችን ብቻ ነበር።
የሊብራል ፓርቲ መሪ ምናልባትም በሌበር ፓርቲ ተቀናቃኛቸው የዳንስታን የምክር ቤት ወንበራቸውን ሊያጡ ይችላሉ።

