ኢትዮጵያዊው አትሌት ሹራ ቂጣታ 40ኛውን የወንዶች ለንደን ማራቶን አሸነፈ

*** አትሌት ሞስነት ገረመው አራተኛ ወጥቷል

Sports

Shura Kitata Source: REU

አትሌት ሹራ ቂጣታ  40ኛውን የወንዶች  ለንደን ማራቶን ሲያሸንፍ ሌላኛው ኢትዮጵያዊ ሲሳይ ለማ ደግሞ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል።

የኢትዮጵያውያ የበላይነት በታየበት የዘንድሮው የወንዶች ውድድር ሙሌ ዋሲሁን 5ኛ እና ታምራት ቶላ ደግሞ 6ኛ ደረጃን አግኝተዋል።

ከአትሌት ኤሉድ ኪፕኦጌ በመቀጠል ውድድሩን የማሸነፍ ቅድመ ግምት አግኝቶ የነበረው አትሌት ሞስነት ገረመው አራተኛ ወጥቷል።

ይህ የለንደን ማራቶን ውድደር በኢትዮጵያውን የበላይነት ተጠናቋል። ለአሸናፊነት ከፍተኛ ግምት ተሰጥቶት የነበረው ኬንያዊው ኪፕቾጌ ሽንፈትን ተጎንጭቷል። ኪፕቾጌ 8ኛ ወጥቷል።

የኤሉድ ኪፕቾጌ ተቀናቃኝ ይሆናል ተብሎ የነበረው ጀግናው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በጉዳት አራሱን ማግለሉ አይዘነጋም።


1 min read

Published

By Demeke Kebede



Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now