አትሌት ሹራ ቂጣታ 40ኛውን የወንዶች ለንደን ማራቶን ሲያሸንፍ ሌላኛው ኢትዮጵያዊ ሲሳይ ለማ ደግሞ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል።
የኢትዮጵያውያ የበላይነት በታየበት የዘንድሮው የወንዶች ውድድር ሙሌ ዋሲሁን 5ኛ እና ታምራት ቶላ ደግሞ 6ኛ ደረጃን አግኝተዋል።
ከአትሌት ኤሉድ ኪፕኦጌ በመቀጠል ውድድሩን የማሸነፍ ቅድመ ግምት አግኝቶ የነበረው አትሌት ሞስነት ገረመው አራተኛ ወጥቷል።
ይህ የለንደን ማራቶን ውድደር በኢትዮጵያውን የበላይነት ተጠናቋል። ለአሸናፊነት ከፍተኛ ግምት ተሰጥቶት የነበረው ኬንያዊው ኪፕቾጌ ሽንፈትን ተጎንጭቷል። ኪፕቾጌ 8ኛ ወጥቷል።
የኤሉድ ኪፕቾጌ ተቀናቃኝ ይሆናል ተብሎ የነበረው ጀግናው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በጉዳት አራሱን ማግለሉ አይዘነጋም።
Share

