በወቅታዊ ወታደራዊ ጉዳዮች ላይ የሌ/ጄኔራል ባጫ ደበሌ መግለጫ

*** ከሽራሮ እስከ ዛላንበሳ ድረስ ያሉት የሰሜን ዝ የጦር ክፍሎች በአሁኑ ሰዓት በጥሩ የዝግጁነት አቋም ላይ ይገኛሉ

Lt. General Bacha Debele

Lt. General Bacha Debele Source: FBC

ሌ/ጄነራል ባጫ ደበሌ ትናንት በወቅታዊ ወታደራዊ ጉዳዮች  ዙሪያ መገለጫ ሰጥተዋል።

ከሽራሮ እስከ ዛላንበሳ ድረስ ያሉትን የሰሜን እዝ የጦር ክፍሎች በአሁኑ ሰዓት በጥሩ የዝግጁነት አቋም ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ ፋና እንደዘገበው

ከሽራሮ እስከ ዛላንበሳ ድረስ ያሉት የሰሜን እዝ የጦር ክፍሎች በአካል አግኝተው መመለሳቸውን ገልጸዋል፡፡

ሌ/ጄኔራል ባጫ ፥ በሰሜን እዝ የመከላከያ ሰራዊት ላይ የተፈጸውን ጥቃት አስመልክተው እንደገለጹት ፣ በሠራዊቱ ውስጥ የነበሩ የህወሓት ተልዕኮ አስፈጻሚዎች ሶስት ተልዕኮ ተሰጥቷቸው ጥቃት ፈፅመዋል ብለዋል ፦

1ኛ. ሠራዊቱን ከውስጥ ማፍረስ፣

2ኛ. ሠራዊቱን መውጋትና

3ኛ. ማዘናጊያ የሽምግልና ስራ መስራት ስለነበር እሱን ተልዕኮ ነው የፈጸሙት ብለዋል።

ሠራዊቱን ከውስጥ ለማፍረስ የሰሜን ዕዝን የሬዲዮ መገናኛ አዲስ አበባ በሚገኘው የመገናኛ ሀላፊ አማካኝነት ወደነሱ አዙረዋል ብለዋል።

እንዲሁም መከላከያና ጦሩ እርስ በርሱ እንዳይገናኝ አድርገዋል ሲሉ ገልፀዋል።

እነዚህ አካላት የሠራዊቱን የወር ደሞዝ እና ቀለቡን ወስደውበታል፣ አዛዦችንም አፍነዋል ብለዋል።

ሌ/ጄኔራል ባጫ ደበሌ ሰራዊቱ ይህ ሁሉ ተፈፅሞበት ተዋግቷቸዋል፣ ጀግንነትም ፈፅሟል ሲሉ ተናግረዋል።

ውጊያው ከክልሉ ልዩ ሀይል ብቻ አልነበረም ያሉት ሌ/ጄኔራል ባጫ ፣ በዛላንበሳ ፣ በሽራሮ ፣ በራማ ፣ በፆረና እና በሌሎች ቦታዎች የኦነግ ሸኔ አባላት ባንዲራቸውን ይዘው አብረው ወግተውናል ብለዋል።

በስፍራው የጦር ሀይሎች ም/ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ሌ/ጀኔራል  አበባው ታደሰ ሠራዊቱን አብረውት እየመሩት እንደሚገኙ በመግለጫው ተጠቅሷል፡፡


1 min read

Published

Updated

By Stringer


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now