በቁጥጥር ስር የዋሉት፤
1- የሕወሓት ቁልፍ ሰው የነበሩት ስብሃት ነጋ
2- ሌተናል ኮሎኔል ፀአዱ ሪች- የስብሃት ነጋ ባለቤትና ቀደም ሲል በጦር ሃይሎች ሆስፒታል ሃኪም የነበረች፣ በኋላም በጡረታ የተገለለች
3- ኮሎኔል ክንፈ ታደሰ- ከመከላከያ የከዳ
4- ኮሎኔል የማነ ካህሳይ- ከመለካከያ የከዳ
5- አስገደ ገ/ ክርስቶስ- ከመሃል ሀገር ተጉዞ ቡድኑን የተቀላቀለና ለጊዜው ሃላፊነቱ ያልታወቀ ግለሰብ
6- አምደማርያም ተሰማ ተወልደ፣ የክልሉ የቅሬታ ሰሚ ፅ/ቤት ኃላፊ የነበረ
7- ኮማንደር በርሄ ግርማ፣ የክልሉ ልዩ ሀይል ሎጀስቲክ ሀላፊ የነበረ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን
8- አልጋነሽ መለስ - የሜጀር ጀነራል ሃየሎም አርአያ ባለቤት የነበረችና ኑሮዋን በአሜሪካ አድርጋ የቆየች በኋላም ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ወደ "ጁንታው" ተቀላቅላ የነበረች፣ በኦፕሬሽን ሂደት ውስጥ ለማምለጥ ስትሞክር ወደ ገደል ወድቃ ህይወቷ ማለፉን ብርጋዴል ጀኔራል ተስፋዬ አያሌው ገልፀዋል።

