በሺዎች የሚቆጠሩ የመንግስት እና ካቶሊክ ት/ቤቶች መምህራን የተሻለ ክፍያን እና የስራን ሁኔታን በመጠየቅ ለሰልፍ ወጡ

ቀያይ ካኒተራዎችን ለብሰው የወጡት ሰልፈኞች በየጊዜው የሚደርሳቸው ሙገሳ ብቻ በቂ ያለመሆኑን ለማሳየት“ ከምስጋና ባላይ ” የሚል መፈክሮችን በጉልህ አሳይተውል ፤ የተሰጣቸውንም 3 በመቶ የደሞዝ ጭማሪ ከስራቸው ጋር ሲነጥጥጸር በቂ ያለምሆኑን ገልጸዋል ።

SBS News in Macedonian 30 June 2022

Teachers march to State Parliament during a strike by NSW public school and Catholic school teachers in Sydney, Thursday, June 30, 2022. Source: AAP Image/Nikki Short

በሺዎች የሚቆጠሩ የመንግስት እና ካቶሊክ ት/ቤቶች መምህራን የተሻለ ክፍያን  እና የስራን ሁኔታን በመጠየቅ ለሰልፍ ወጡ ። ሰልፈኞቹ ከኒው ሳውዝ ዌል በመነሳት ወደ ካንብራ አቅንተዋል ።

የኒውሳውዝ ዌልስ የመምህራን ፌዴሬሽን እና የገለልተኛ ትምህርት ህብረት አውስትራሊያ ፤ በጣምራ በመሆን፤ ሰልፉ በጁን 30 ጀምሮ ለ 24 እንዲደረግ በጋራ ውሳኔ ላይ በመድረሳቸውም ነው ሰልፉ የተጠራው።

ቀያይ ካኒተራዎችን ለብሰው የወጡት ሰልፈኞች በየጊዜው የሚደርሳቸው ሙገሳ ብቻ በቂ ያለመሆኑን ለማሳየት“ ከምስጋና ባላይ ” የሚል መፈክሮችን በጉልህ  አሳይተውል ፤ የተሰጣቸውንም 3 በመቶ የደሞዝ ጭማሪ ከስራቸው ጋር ሲነጥጥጸር በቂ ያለምሆኑን ገልጸዋል ።

የኒውሳውዝ ዌልስ የመምህራን ፌዴሬሽን ጭማሪም ከ 5 እስክ 7 በመቶ እንዲሆን ጥያቄ አቀርቧል ።

ባልፉት ስድስት ወራት ለሶስተኛ ጊዜ በተጠራው ሰልፍ ከ 85፣000 በላይ መምህራን ተሳትፈዋል ።

እንዲህ ያለን ሰልፍን ሁለቱ ህብረቶች በጋራ ሲያዘጋጁ በ 25 አመት ታሪክ ውስጥ የመጀመሪያው እንደሆነ ተነግሮለታል ።

የትምህርት ምኒስትሯ ሳራ ሚቸል ሰልፉ በመካሄዱ የተሰማቸውን ቅሬታን ድርጊቱ ከፖለቲካ አጀንዳ ጋር የተያያዘ ነው ሲሉ ገልጸውታል ።አያይዘውም መንግስት ለህዝብ አገልጋዮች የሚከፍለው ክፍያ የተሻለ ነው ሲሉ የሰልፈኞቹን የደሞዝ ጭማሪ ጥያቄ አጣጥለውታል ።


1 min read

Published

Source: Source: AAP, SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now