የ2013 ምርጫ ጣቢያዎች ዝርዝር ይፋ ሆነ

*** ለ6ተኛው ጠቅላላ ምርጫ 49,407 የምርጫ ጣቢያዎች አገልግሎት የሚሰጡ ይሆናል።

NEBE: Voting sites

Birtukan Mideksa, Chairperson of the National Election Board of Ethiopia. Source: Getty

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የካቲት 03 ቀን 2013 ዓ.ም የምርጫ ጣቢያዎችን ዝርዝር ይፋ አድርጓል።

ምርጫ ቦርድ ባወጣው 6ተኛው አገር አቀፍ የምርጫ ሰሌዳ ላይ በተገለጸው መሰረት የካቲት 03 ቀን የምርጫ ጣቢያዎች ዝርዝር ይፋ ማድረጊያ ቀን ነው።

ቦርዱ የምርጫ ምልክት በመውሰድ ለምርጫ ለመወዳደር ዝግጅት እያደረጉ ያሉ ሁሉም ፓርቲዎች የምርጫ ጣቢያዎቹን ዝርዝር በፍላሽ እንዲደርሳቸው ያደረገ ሲሆን በተጨማሪም በድረ-ገጹ ላይ አስፍሯል።

በዚህ መሠረት:-

✔በአዲስ አበባ ከተማ - 1,848

✔በሲዳማ ክልል - 2,247

✔ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል - 699

✔አፋር ክልል- 1,432

✔አማራ ክልል- 12,199

✔ድሬዳዋ ክልል- 305

✔ጋምቤላ ክልል- 431

✔ሃረሪ ክልል- 285

✔ኦሮሚያ ክልል- 17,623

✔ደ/ብ/ብ/ህ ክልል- 8,281

✔ሶማሌ ክልል- 4,057

በአጠቃላይ 49,407 የምርጫ ጣቢያዎች ለ6ተኛው ጠቅላላ ምርጫ አገልግሎት የሚሰጡ ይሆናል። 

 

 


1 min read

Published

By Stringer Report


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now