የ 'Black Lives Matter' - BLM ሕዝባዊ ንቅናቄ የዘር ኢ-ፍትሐዊነትን በመፋለም ረገድ "በመላው ዓለም ያካሔደው ንቅናቄ በጣሙን ጠቃሚ ነው" በሚል አመኔታ በኖርዌይ ፓርላማ አባል ፒተር ኢድ በሰብዓዊ ክብር ዘርፍ ለኖቤል ሰላም ሽልማት ታጭቷል።
የሕዝባዊ ንቅናቄውን ሂደት አስመልክተው ሲናገሩም "ጥናቶች እንደሚያሳዩት አብዛኛዎቹ በብላክ ላይቭስ ማተር የተካሄዱት ሰልፎች ሰላማዊ ነበሩ" ብለዋል።
አያይዘውም " እርግጥ ነው፤ ግጭቶች ነበሩ። ሆኖም አብዛኛዎቹ የተከሰቱት አንድ በፖሊስ አለያም በጸረ-ሰላማዊ ሰልፈኞች ነው" ሲሉ ተናግረዋል።
እንደ የትጥቅ ግጭት አካባቢና ኩነት ዳታ ፕሮጄክት የሴፕቴምበር ጥናት መረጃ መሠረት ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ከተካሄዱት ሰልፎች ውስጥ 93 ፐርሰንቱ ሰላማዊ ነበሩ።

የኖቤል ሰላም ሽልማት ኮሚቴ የዕጩዎች ጥቆማ መቀበልን በፌብሪዋሪ 1 ያቆማል፣ በማርች ሁነኛ ተፎካካሪ ያላቸውን ዕጩዎች ይወስናል፤ በኦክቶበር ከዕጩዎቹ መካከል አሸናፊ ያለውን መርጦ በማስታወቅ ዲሴምበር 10 የሽልማት ሥነ ሥርዓቱን ያካሂዳል።
ባለፈው ዓመት 300 ዕጩዎች ለኖቤል ሰላም ሽልማት ቀርበው ነበር።

