የተባበሩት መንግሥታት የዓለም ምግብ ፕሮግራም የዘንድሮው የኖቤል ሰላም ሽልማት አሸናፊ ሆኗል።
የዓለም ምግብ ፕሮግራም ለአሸናፊት የበቃው ረሃብና የምግብ ዋስትና እጥረትን በመላው ዓለም በመፋለም ላበረከታቸው ጥረቶቹ ነው።
ሽልማቱን ከኦስሎ ይፋ ያደረጉት የኖቤል ኮሚቴ ሰብሳቢ ቤሪት ሪስ-አንደርሰን ይህንኑ አስመልክተው ሲናገሩ "በዚህ ዓመት ሽልማት የኖቤል ሰላም ሽልማት ኮሚቴ የዓለምን ዓይኖች በረሃብ እየተሰቃዩ ወይም ተጋልጠው ያሉቱ ሚሊየን ሰዎች ላይ እንዲያርፉ ይፈልጋል"
"የዓለም ምግብ ፕሮግራም የምግብ ዋስትናን የሰላም መሳሪያ በማድረግ በመልቲዮሽ ትብብር ቁልፍ ሚና ተጫውቷል" ብለዋል።
ለዘንድሮው የኖቤል ሰላም ሽልማት በተወዳዳሪነት የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕንና የኒውዝላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ጃሲንዳ አርደንን አካትቶ 211 ግለሰቦችና 107 ድርጅቶች ቀርበዋል።
የዓለም ምግብ ፕሮግራም ዲሴምበር 10 - 2020 በሚካሄደው የሽልማት አሰጣጥ ሥነ ሥርዓት ወቅት 10 ሚሊየን ክሮና ወይም $1.1 ሚሊየን ጥሬ የአሜሪካን ዶላርስና የወርቅ ሜዳል ይቀበላል።
የዓለም ምግብ ፕሮግራም 97 ሚሊየን ሰዎችን በ88 አገራት በየዓመቱ እየረዳ ቢሆንም አሁንም በመላው ዓለም ከዘጠኝ ሰዎች አንዳቸው የሚመገቡት በቂ ምግብ የሌላቸው መሆኑን አስታውቋል።

