የጠቅላይ ሚኒስትሩ የካንብራ መኖሪያ ቤት በፖሊስ ፍተሻ ሲደረግበት ቆይቷል።
የአውስትራሊያ ፌዴራል ፖሊስ ምንም እንኳ ቀደም ሲል የደህንነት ስጋት ያሳደረ ሁኔታ አለ የሚል ማስጠንቀቂያ የደረሰው ቢሆንም፤ በፍተሻው ምንም አስጊ ሁኔታ ባለመከሰቱ አቶ አልበኒዚ ከምሽቱ 9:00pm ወደ መኖሪያቸው እንዲመለሱ መደረጉን አስታውቋል።
አክሎም "በአሁኑ ወቅት በሕዝብ ወይም በማኅበረሰብ አባላት ላይ የተደቀነ ስጋት የለም። ተጨማሪ መረጃዎች አስፈላጊ በሆነ ጊዜ ይሰጣል" ብሏል።
በቅርብ ወራት ውስጥ ጠቅላይ ሚኒስትሩና በርካታ የምክር ቤት አባሎች ላይ ዛቻዎች ተሰንዘረዋል።
Share

