"ኢትዮጵያ ወደ ትርምስ ትገባለች የሚለው ስጋት የአገሪቷን ነባራዊ ሁኔታ በጥልቀት ካለመረዳት የመነጨ ነው" - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ

***" አሁን እየተካሄደ ያለው ህግ የማስከበር ስራ ሰላምንና መረጋጋትን በማስፈን ወንጀለኞችን ለHግ ለማቅረብ ያለመ ነው" ዐቢይ አሕመድ

PM Abiy Ahmed

PM Abiy Ahmed Source: PMOE

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተለያዩ ወገኖች ኢትዮጵያ ወደ ትርምስ ትገባለች የሚለው ስጋታቸው የማይሆን እና የሃገሪቷን ነባራዊ ሁኔታ በጥልቀት ካለመረዳት የሚመነጭ ነው ሲሉ ተናገሩ፡፡

 ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትዊተር ገጻቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ የኢትዮጵያ ወዳጆች በሃገሪቱ ስላለው ሁኔታ ለሰጡት ትኩረት መንግስት ደስተኛ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

 ይሁን እንጅ ኢትዮጵያ ወደ ትርምስ ትገባለች የሚለው ስጋታቸው የማይሆን እና የሃገሪቷን ነባራዊ ሁኔታ ካለመረዳት የመነጨ መሆኑንም ነው የጠቀሱት፡፡

 አሁን እየተካሄደ ያለው ህግ የማስከበር ስራ ሰላምንና መረጋጋትን በማስፈን ወንጀለኞችን ለህግ ለማቅረብ ያለመ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ህግ የማስከበሩ ተልዕኮ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅም ገልጸዋል፡፡


1 min read

Published

By Abiy Ahmed


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now