ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተለያዩ ወገኖች ኢትዮጵያ ወደ ትርምስ ትገባለች የሚለው ስጋታቸው የማይሆን እና የሃገሪቷን ነባራዊ ሁኔታ በጥልቀት ካለመረዳት የሚመነጭ ነው ሲሉ ተናገሩ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትዊተር ገጻቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ የኢትዮጵያ ወዳጆች በሃገሪቱ ስላለው ሁኔታ ለሰጡት ትኩረት መንግስት ደስተኛ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ይሁን እንጅ ኢትዮጵያ ወደ ትርምስ ትገባለች የሚለው ስጋታቸው የማይሆን እና የሃገሪቷን ነባራዊ ሁኔታ ካለመረዳት የመነጨ መሆኑንም ነው የጠቀሱት፡፡
አሁን እየተካሄደ ያለው ህግ የማስከበር ስራ ሰላምንና መረጋጋትን በማስፈን ወንጀለኞችን ለህግ ለማቅረብ ያለመ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ህግ የማስከበሩ ተልዕኮ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅም ገልጸዋል፡፡
Share

