በምዕራብ ወለጋ ዞን ጉሊሶ ወረዳ በሰላማዊ ዜጎች ላይ የደረሰውን ግድያ አስመልክቶ ፕሬዚደንት ሳሕለወርቅ ዘውዴ የልባቸውን በኃዘን መሰበርና የሕግ የበላይነት መከበርን ግድ ማለት ያሰመረ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
"የሰማሁት ዜና ልቤን ሰብሮታል ብል ማጋነን አይሆንም፡፡ የዛሬ አመት የተናገርኩት ከመድገም ዉጪ ሌላ ቃላት የለኝም፡፡
"ዘርና ሀይማኖት ለፖለቲካ ጥቅም እንዲውሉ ሲደረግ፤ ንጹሀን ዜጎቻችን በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገደሉ፣ ሲፈናቀሉና ሲንከራተቱ ስናይ ስሜትን ለመግለጽ ቃላት ያጥራል: ለቅሶ፣ድንጋጤና ሥጋት የብዙዎችን በር አንኳኩቷል ሃዘናቸው ሃዘኔ/ሃዘናችን ነው::
ለሀገርና ለህዝብ ጥቅም ሲባል ልናሰምረው እና ልናከብረው የሚገባን ቀይ መስመር ተጥሷል፡ አገራችንን ካንዣበበባት ክፉ አዳጋ ለማዳን ሁላችንም ሚና አለን፡የሚመለከታቸው ሁሉ የበኩላቸውን መወጣት አለባቸው፡ቀይ መስመር መጣስ የለበትም እንበል::"

