Latest

ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ ለአውስትራሊያዊቷ ድምፃዊት ጁዲት ዱርሃም ሕልፈተ ሕይወት ሐዘናቸውን ገለጡ

በአውስትራሊያ የቻይና ኤምባሲ አውስትራሊያ ከዩናይትድ ስቴትስ - ታይዋን ውዝግብ ራሷን እንድታገል አሳሰበ።

 Royal Festival Hall.jpg

ROYAL FESTIVAL HALL Photo of Judith DURHAM- 3rd July 2003. Source: Getty / C Brandon/Redferns

የአውስትራሊያ ሙዚቃ ኢንዱስትሪ በፅኑ የሳምባ ሕመም በ79 ዓመቷ ለህልፈተ ሕይወት ለበቃችው ድምፃዊት ጁዲት ዱርሃም ሐዘኑን በመግለጥ ላይ ነው።

የጁዲት እህት ቤቨርሊ ሺሃን ጁዲት በሕይወት ተደሳች፣ ሁሌም በተስፋ የተመላችና ቸር እንደነበረች ተናግራለች።

ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚም በበኩላቸው ጁዲት የአገር ቅርስና የአውስትራሊያ መለያ መሆኗን ሐዘናቸውን በገለጡበት ወቅት ጠቅሰዋል። 
 
ጁዲት የተወለደችው ኢሰንደን - ቪክቶሪያ ነበር።

***
በአውስትራሊያ የቻይና ኤምባሲ አውስትራሊያ ከዩናይትድ ስቴትስ - ታይዋን ውዝግብ ራሷን እንድታገል አሳሰበ።

ኤምባሲው በቤጂንግ ላይ ጣትን መጠቆም ተቀባይነት እንደሌለውም አስገንዝቧል።

 ለኤምባሲው ማሳሰቢያ አስባብ የሆነው የአውስትራሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፔኒ ዎንግ የዩናይትድ ስቴት ስ አፈ ጉባኤ የታይዋን ጉብኝት አስመልክቶ ቻይና የወሰደችው እርምጃ "ተመጣጣኝ ያልሆነ" እና "መረጋጋትን አደፍራሽ" ነው ማለታቸውን ተከትሎ ነው።

ሴናተር ዎንግ በአሁኑ ወቅት ከቻይናው አቻቻእው ዋንግ ዪ ጋር በካምቦዲያ የደቡብ ምሥራቅ እስያ አገራት ማኅበራት 47ኛ ጉባኤ ላይ በመሳተፍ ይገኛሉ።

 



 












Share

Published

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service