የኢደንብራው መስፍን ልዑል ፊሊፕ ያደረባቸው ሕመም ፀንቶባቸው ባለፈው ወርኃ ፌብሪዋሪ ሆስፒታል ገብተው ሕክምና ሲከታተሉ ነበር።
ልዑል ፊሊፕ ሕይወታቸው ያለፈው ዛሬ ዓርብ በአውስትራሊያ ሰዓት አቆጣጠር አመሻሽ ላይ ነው።
የባኪንግሃም ቤተመንግሥት ባወጣው መግለጫ
"ንግሥት ኤልሳቤጥ የተፈቃሪ ባለቤታቸውን የኢደንብራ መስፍን ልዑል ፊሊፕ ሕልፈተ ሕይወት ሲገልጡ በጥልቅ ኃዘን ነው"
"ልዑልነታቸው ለሕልፈተ ሕይወት የበቁት ዊንድዞር ካስትል በሰላማዊ ሁኔታ ነው"
"ተጨማሪ መግለጫዎች በሂደት ይሰጣሉ"
"የንግሥታዊው ቤተሰብ በመላው ዓለም በእሳቸው ሕልፈት ከሚያዝኑት ጋር አብረው ያዝናሉ" ብሏል።
ልዑል ፊሊፕ ከንግሥት ኤልሳቤጥ ጋር ለ73 ዓመታት በጋብቻ ኖረዋል።
የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰንና የአውስትራሊያው ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን ኃዘናቸውን ገልጠዋል።ልዑል ፊሊፕ ያደረባቸው ሕመም ፀንቶባቸው ባለፈው ወርኃ ፌብሪዋሪ ሆስፒታል ገብተው ሕክምና ሲከታተሉ ነበር።
ልዑል ፊሊፕ ሕይወታቸው ያለፈው ዛሬ ዓርብ በአውስትራሊያ ሰዓት አቆጣጠር አመሻሽ ላይ ነው።
የባኪንግሃም ቤተመንግሥት ባወጣው መግለጫ
"ንግሥት ኤልሳቤጥ የተፈቃሪ ባለቤታቸውን የኢደንብራ መስፍን ልዑል ፊሊፕ ሕልፈተ ሕይወት ሲገልጡ በጥልቅ ኃዘን ነው"
"ልዑልነታቸው ለሕልፈተ ሕይወት የበቁት ዊንድዞር ካስትል በሰላማዊ ሁኔታ ነው"
"ተጨማሪ መግለጫዎች በሂደት ይሰጣሉ"
"የንግሥታዊው ቤተሰብ በመላው ዓለም በእሳቸው ሕልፈት ከሚያዝኑት ጋር አብረው ያዝናሉ" ብሏል።
ልዑል ፊሊፕ ከንግሥት ኤልሳቤጥ ጋር ለ73 ዓመታት በጋብቻ ኖረዋል።
የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰንና የአውስትራሊያው ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን ኃዘናቸውን ገልጠዋል።

