ታዋቂው ኢትዮጵያዊ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም መስከረም 19 - 2013 ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
የፕሮፌሰር መስፍንን ሕልፈተ ሕይወት አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቲዊተር ገጻቸው "የሐሳብ ልዕልና ምልክት፤ የሰላማዊ ትግል አርአያ፣ ላመኑበት ነገር እስከ መጨረሻቸው ሞጋች፣ ላመኑበት እውነት ብቻ የሚቆሙት ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም በማረፋቸው ጥልቅ ኀዘን ተሰምቶኛል። ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን እመኛለሁ" ብለዋል።
በአያሌ ወዳጆቻቸውና አድናቂዎቻቸው ዘንድ "ጋሼ" ተብለው የሚጠሩት ፕ/ር መስፍን የጂኦግራፊ ተጠባቢ፣ ደራሲ፣ የኢትዮጵያ ሰብ ዓዊ መብቶች ጉባኤ መሥራችና መሪ የነበሩ ናቸው።
Share

