ኢትዮጵያዊው ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ከዚህ ዓለም በሕልፈተ ሕይወት ተለዩ

*** "የሃሳብ ልዕልና ምልክት፣ የሰላም ትግል አርአያ…" ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አንደበት

Mesfin Woldemariam

Prof Mesfin Woldemariam Source: PD

ታዋቂው ኢትዮጵያዊ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም መስከረም 19 - 2013 ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

የፕሮፌሰር መስፍንን ሕልፈተ ሕይወት አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቲዊተር ገጻቸው "የሐሳብ ልዕልና ምልክት፤ የሰላማዊ ትግል አርአያ፣ ላመኑበት ነገር እስከ መጨረሻቸው ሞጋች፣ ላመኑበት እውነት ብቻ የሚቆሙት ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም በማረፋቸው ጥልቅ ኀዘን ተሰምቶኛል። ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን እመኛለሁ" ብለዋል።

በአያሌ ወዳጆቻቸውና አድናቂዎቻቸው ዘንድ "ጋሼ" ተብለው የሚጠሩት ፕ/ር መስፍን የጂኦግራፊ ተጠባቢ፣ ደራሲ፣ የኢትዮጵያ ሰብ ዓዊ መብቶች ጉባኤ መሥራችና መሪ የነበሩ ናቸው።

 


1 min read

Published

By Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now