የፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያምን ራዕይና ስራዎች የሚያስቀጥል ፋውንዴሽን ተመሠረተ።
የኘሮፌሰሩ ዕረፍት አንደኛ አመት መታሰቢያና የፋውንዴሽኑን ምስረታ አስመልክቶ አዘጋጅ ኮሚቴው ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
በዚህ ወቅት የፋውንዴሽኑ ሊቀመንበር ዶክተር በድሉ ዋቅጅራ እንዳሉት ፕሮፌሰር መስፍን ሙሉ ህይወታቸውን ለአገር የሰጡ ናቸው።
ፕሮፌሰሩ ኢትዮጵያ ከድህነት የተላቀቀች፣ ሰላም፣ ሰብአዊ መብትና የሕግ የበላይነት የሰፈነባት ለማድረግ ሲሰሩ እንደነበር ገልፀዋል።
በስማቸው የተመሰረተው ፋውንዴሽን በማኅበረሰብ ሳይንስና በሠብዓዊ መብት ላይ ምርምር ለሚያካሂዱ ዜጎች ድጋፍ እንደሚያደርግ ተነግሯል።
ፋውንዴሽኑ ዓመታዊ አውደ ጥናት በማዘጋጀት የጥናትና ምርምር ስራዎች እንዲካሄዱ ያደርጋልም ተብሏል።
(ኢዜአ)
Share

