የአውስትራሊያ ተቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን ዛሬ እሑድ ኤፕሪል 21 አገር አቀፍ የምርጫ ቀን ሜይ 21 እንዲካሔድ ቀን መቁረጣቸውን አስታወቁ።
አውስትራሊያውን ምርጫቸው በሚያካሒዱበት ወቅት ለ151 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትና 40 የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት አባላት ድምፃቸውን ይሰጣሉ።

በአሁኑ ወቅት የጥምር መንግሥቱ 76 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወንበሮች ይዞ ያለ ሲሆን መንግሥት ለመመሥረት ተቀናቃኝ ሆኖ ያለው ሌበር ፓርቲ 68 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወንበሮችን ይዟል።
የግሪንስ ፓርቲ አንድ፤ የግል ተመራጮች ሶስት የሕዝብ ምክር ቤት ወንበሮችን ይዘው ይገኛሉ።
Share

