በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ሁለኛ ዙር ሙሌት ግብፅ የተቃውሞ ድምፅ አሰማች

*** የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ፀጥታ ምክር ቤት በሕዳሴ ግድብ ላይ ሐሙስ ይወያያል

GERD

GERD. Source: S.Bekele

ግብፅ ከኢትዮጵያ የሁለተኛ ዙር ሕዳሴ ግድብ ሙሌት ጅማሮን አስመልክቶ ይፋ ደብዳቤ እንደደረሳት ጠቅሳ በውኃው ሙሌት ላይ ያላትን ተቃውሞ ገልጣለች።

የሁለተኛው ዙር ሙሌት ጅማሮ የፊታችን ሐሙስ ጁላይ 8 በተመድ ፀጥታ ምክር ቤት ላይ የሚነሳውን የሕዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር ጉዳይ ላይ ተጨማሪ ውጥረትን ያሳድራል ተብሎ ተገምቷል። 

ግብፅና ሱዳን በሕዳሴ ግድብ ላይ ሕጋዊ አስገዳጅነት ያለው ውል ከኢትዮጵያ ጋር መፈራረም ይሻሉ።

ይሁንና የሁለቱ አገራት ሕጋዊ አስገዳጅነት ያለ ውል ተደጋጋሚ ጥያቄ በኢትዮጵያ በኩል በተደጋጋሚ ተቀባይነት አላገኘም።

በኢትዮጵያ በኩል የድርድሩ ሂደት በአፍሪካ ኅብረት በኩል እንዲካሄድና ዕልባት እንዲያገኝ የምትሻም ቢሆን ጉዳዩ በፀጥታውን ምክር ቤት ተነስቶ ይመከርበታል።

የሕዳሴ ግድብ ጉዳይ ለፀጥታው ምክር ቤት እንዲቀርብ በግብፅና ሱዳን ስም ጥሪ ያቀረበችው ቱኒዝያ ናት።

UN Security Council meeting.
UN Security Council meeting. Source: Getty

የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር ውኃ ሙሌት ጉዳይ በፀጥታ ምክር ቤቱ እንዲነሳ መነሳትን አስመልክቶ የወቅቱ የወርኃ ጁላይ የተመድ ፀጥታ ምክር ቤት ፕሬዚደንትና በተመድ የፈረንሳይ አምባሳደር ኒኮላስ ዴ ሪቪዪሬ ባለፈው ሳምንት ሲናገሩ "የፀጥታ ምክር ቤቱ ማድረግ የሚችለው ነገር ትንሽ ነው። አገራቱን አገናኝቶ ስጋቶቻቸውን በጋራ እንዲገልጡ ከማድረግና ከስምምነት ላይ ለመድረስ ወደ ድርድር እንዲመለሱ ከማበረታት ባሻገር መከወን የሚችለው ነገር የለም" ሲሉ ለሪፖርተሮች ገልጠዋል።     

ኢትዮጵያ በወርኃ ጁላይ ሙሌት 13.5 ኪዩቢክ ሜትር ውኃ ለማቋር ትልም አላት።

   


1 min read

Published

Updated

By Stringer Report


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now