የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ እሑድ ባወጣው መግለጫ የኤርትራ መዲና አሥመራ ላይ ስድስት ፍንዳታዎች መከሰታቸውን አስታውቋል።
ይሁንና "ኖቬምበር 28 ስድስት ፍንዳታዎች አሥመራ ውስጥ 10:30 p.m ላይ ተከስቷል" ያለው የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ መግለጫ ደረሱ ስላላቸው ፍንዳታዎች መንሰኤና ሥፍራዎቹን አልጠቀሰም።
ሆኖም አሜሪካውያን ኢትዮጵያ ውስጥ በትግራይ ክልል እየተካሄድ ስላለው ሁኔታ ልብ እንዲሉ አሳስቧል።
ቀደም ባሉት ሳምንታት ለሁለት ጊዜያት ያህል በሕወሓት የተወነጨፉ ሮኬቶች አሥመራ ላይ ጥቃት ማድረሳቸው የሚታወስ ነው።
ለጊዜው ከኤርትራ መንግሥት በኩል ይፋ መግለጫ አልተደመጠም።
Share

