ግዙፉ ሉላዊ የማኅበራዊ ሚዲያ ኩባንያ ፌስቡክ ብሔራዊ ጥቅሞቼን የተጋፋ ድርጊት ፈጽሟል ኢትዮጵያ በማለት የራሷን ማኅበራዊ ሚዲያ አውታረ መረብ ለመዘርጋት በሂደት ላይ መሆኑን አስታወቀች።
የማኅበራዊ ሚዲያ የመዘርጋቱን ዕቅድ ለአገር ውስጥ ዘጋቢዎች የገለጡት የመንግሥት የመረጃ አውታረ መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ዳይሬክተር ሹመት ግዛው ናቸው።
ዳይሬክተሩ 'ፌስቡክና ትዊተር ለፖለቲካ ኃይሎች መሳሪያነት' እየዋሉ እንደሁ ጠቁመው ኢትዮጵያ የዋትስኧፕ የመልዕክት ፕሮግራምንና የዙም የቪዲዮ ኮንፈረንስ መድረክን' ለመተካት በመሰናዶ ሂደት ላይ መሆኗን ተናግረዋል።

