ቪክቶሪያ ውስጥ የኮሮናቫይረስን መስፋፋት ለማዘግየት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተራዘመ

ቪክቶሪያ ውስጥ እየተስፋፋ ያለውን የኮሮናቫይረስ ወረርሽ ለመቀነስ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ለአራት ሳምንታት እንዲራዘም ተደርጓል። በዚህም መሠረት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እስከ ጁላይ 19 - 2020 እኩለ ለሊት ድረስ የጸና ይሆናል።

STATE OF EMERGENCY EXTENDED TO KEEP SLOWING THE SPREAD

Source: Courtesy of VSG

በእኒህ ጊዜያት ውስጥም የቪክቶሪያ ፖሊስ አካላዊ ርቀትንና ወሸባ ገብቶ የመቆየት ድንጋጌዎችን የማስፈጸም ሥልጣኑን ይጠቀማል።

 

ይህንንም ለማከናወን 500 የፖሊስ ሠራዊት አባላት ይሠማራሉ።

 

ድንጋጌዎቹን ተላልፈው የሚገኙ ግለሰቦች እስከ $1,652 የንግድ ተቋማት እስከ $9,913 መቀጮ ይጣልባቸዋል።

 

 

ይህንንም ጥሰው የሚገኙ ግለሰቦች፤ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መሠረ ፍርድ ቤት ቀርበው እስከ $20,000 ኩባንያዎች እስከ $100,000 ዶላርስ ይቀጣሉ።

 

የቪክቶሪያ መንግሥት መልዕክቱን በድጋሚ አበክሮ ሲያስገነዘብ  "አካላዊ ርቀትን ጠብቁ። ከመጨባበጥና መተቃቀፍ ተቆጠቡ። ሥነ ንጽሕናን በመጠበቁ ቀጥሉ። ምግብና መጠጥን ተጋርታችሁ አትመገቡ፤ አትጠጡ። ጤና ካልተሰማችሁ ከቤት አትውጡ፣ ጓደኞችና ቤተሰቦችን ሔዳችሁ አትጠይቁ፣ ሽርሽር አትሂዱ፣ ወደ ሥራ አትግቡ፣ ቤት ውስጥ ቆዩ" ብሏል።


1 min read

Published

Updated

Presented by Kassahun Seboqa Negewo



Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now