ሽልማቱ በባህር ዳር ጣና ሃይቅ የተካሄደ ሲሆን፣ የዘንድሮ ሽልማቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተከሰተውን የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ከዚህ ቀደም ከነበሩት ዘርፎች በመቀነስ በጤና እና በጣና ዙሪያ በተለያዩ ዘርፎች በማቀናጀት ዕውቅናና ሽልማት የመስጠት ሥነ ሥርዓት ተከናውኗል።

በዚህም መሰረት በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ኢዘዲን ከሚል፣ በጤና መረጃ - ሸጋው ማሬ፣ በፈጣን፣ በወቅታዊ እና ሚዛናዊ መረጃ- ደመቀ ከበደ፣ በጣና ሃይቅ አካባቢ ልማት መረጃ ዘርፍ- ተዋቸው ደርሶ፣ በበጎ አድራጎትና በሰብዓዊ መብት መረጃ- ኦባንግ ሜቶ እና ኡስታዝ አቡበከር አህመድ፣ በጤና ዘርፍ በተቋም ደረጃ ልዩ ተሸላሚ- የአማራ ክልል ጤና ጥበቃ ቢሮ ተሸላሚ ሆነዋል።

የሰብዓዊ መብት መረጃ ዘርፍ ተሸላሚው ኦባንግ ሜቶ በሽልማቱ ወቅት ባደረጉት ንግግር “ጣናን ከእንቦጭ ራሳችንን ከጥላቻና ዘረኝነት ማጽዳት ይኖርብናል” ብለዋል፡፡

