ጉባኤው " ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል መሪ ሀሳብ ነው በመካሄድ ላይ ያለው።
መሪዎቹ የሚመክሩት 48ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አሥፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብስባ ላይ ውይይት በተደረገባቸው አጀንዳዎች ላይ ነው።
የውሃ ደህንነት እና የንጽህና፣ አጠባበቅ፣ የአጀንዳ 2063 ትግበራን እና አህጉራዊ ትስስር፣ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ልማት፣ የሰው ኃይል ልማት፣ ተቋማዊ እና የፋይናንስ ማሻሻያዎች፣ ቀጣናዊ አጋርነት እና አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና ከአጀንዳዎቹ መካከል ይጠቀሳሉ።
39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች መደበኛ ጉባኤ እስከ ነገ የሚካሄድ ይሆናል።
ትናንት ምሽት የኢትዮጵያ መንግሥት ለተሳታፊዎች በብሔራዊ ቤተ መንግስት የእንኳን ደህና መጣችሁ የእራት ግብዣ አከናውኗል።
( ደመቀ ከበደ ፡ ከአፍሪካ ሕብረት )

