በኢቢኤስ ዘገባ መሠረት አቶ አማን ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ረቡዕ የካቲት 4 ቀን 2018 ከእዚህ ዓለም ተለይተዋል።
አቶ አማን የኢትዮጵያ ብሬድካስተሮች ማኅበር ፕሬዚዳንት ሆነው ሲያገለግሉም ቆይተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኢቤኤስ ቴሌቪዥን ዋና ሥራ አሥፈጻሚ እና መስራች አማን ፍስሃጽዮን ሕልፈተ ሕይወት የተሰማቸውን ሐዘን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት የሐዘን መልዕክት÷ 'የኢቢኤስ ቴሌቪዥን መሥራች እና ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አማን ፍስሃጽዮን በማረፉ ኀዘን ተሰምቶኛል' ብለዋል፡፡
አማን ለኢትዮጵያ የግል ሚዲያ ዕድገት ወሳኝ ሚና ከነበራቸው አንዱ ነው በማለት አስታውሰዋል።
'ኢትዮጵያ በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ባለፈች ጊዜ ሁሉ የሚጠበቅበትን አድርጓል' በማለት አውስተዋቸዋል፡፡

