ትዕግስት ገዛኸኝ ለኢትዮጵያ በታሪክ የመጀመሪያውን የፓራሊምፒክ የወርቅ ሜዳል አስገኘች

*** "ኢትዮጵያ ኮርታብሻለች" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለትዕግስት

Tokyo 2020 Paralympic Games

Tigist Gezahagn Menigstu of Ethiopia celebrates after winning the T13 Women's 1500 metre final at the Olympic Stadium on day four. Source: Getty

ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትዕግስት ገዛኸኝ መንግሥቱ በቶኪዮ ፓራሊምፒክ 2020 የሴቶች 1500 T13 ምድብ 4:23.24 በመጨረስ ለኢትዮጵያ በታሪክ የመጀመሪያ የሆነውን የወርቅ ሜዳል አስገኝታለች።

የትዕግስትን ታሪካዊ የፓራሊምፒክ ድል አስመልክተው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ "ትዕግስት ገዛሀኝ መንግሥቱ በሴቶች 1,500 በማሸነፍና በፓራሊምፒክ ውድድር የወርቅ ሜዳልያ ለማስገኘት #በኢትዮጵያ የመጀመሪያዋ አትሌት በመሆኗ እንኳን ደስ ያለሽ። #ኢትዮጵያ ኮርታብሻለች!" ብለዋል።

በዚሁ ቅዳሜ ኦገስት 28 ምሽት በብሔራዊ ኦሎምፒክ ስታዲየም በተካሄደው የአራተኛ ቀን ውድድር የ21 ዓመቷን ትዕግስትን ተከትለው የዩናይትድ ስቴትሷ ሊዛ ኮርሶ ሁለተኛ፤ የቱኒዚያዋ ሶማያ ቦዩሳድ ሶስተኛ ሆነው የብርና የነሐስ ሜዳል አሸናፊዎች ሆነዋል።

ትዕግስት ባስገኘችው የወርቅ ሜዳል ኢትዮጵያ በሜዳል ሠንጠረዥ 48ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።

አውስትራሊያ 7 የወርቅ 10 የብር 11 የነሐስ በጥቅሉ 28 ሜዳሊያዎችን በአሸናፊነት በማግኘት በሜዳል ሠንጠረዥ 5ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።

በግንባር ቀደም የሜዳል ሠንጠረዥ ቻይና በአጠቃላይ 77 ፣ እንግሊዝ 43 ፣ የሩስያ ፓራሊምፒክ ኮሚቴ 41 ሜዳሊያዎችን በማግኘት  በመሪነት ደረጃ ላይ ይገኛሉ። 

 


1 min read

Published

By Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now